Loading...

ስለ ሐበሻ የኦንላይን ት/ቤት

ትምህርት ቤቱ የሚገኘው ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ውስጥ ነው። የሚሰጠውም አገልግሎት በኦንላይን የተለያዩ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ እንዲሁም እንግሊዝኛ ቋንቋዎችን በተጨማሪም ሂሳብ እና የኮምፒውተር ትምህርትን እንሰጣለን። ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታዮች ውዳሴ ማርያም በግእዝ ከነ ዜማ እና የተለያዩ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ትምህርቶችን በተለያዩ ክፍሎች ከፋፍለን በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስተማሪዎች የምንሰጥ ሲሆን በአካል ትምህርቶቹን ማግኘት ለማይችሉ ከሀገር ውጪም ሆነ ሀገር ውስጥ ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ልጆችም ሆነ አዋቂዎች የተዘጋጀ ነው።

የቋንቋ ትምህርቶቹ ልጆች ወደ ሀገራቸው ሲመጡ ከኢትዮጵያ ጓደኞቻቸውም ሆነ ቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲግባቡ የሚረዳቸው ሲሆን የሐበሻ ኦንላይን ት/ቤት ተማሪዎች የተለያዩ የአለም ሀገራት ስብስብ በመሆናቸው ተማሪዎች ከጓደኞቻቸው የተለያየ መረጃ ፣ ሀሳብ እና እውቀት እንዲጋሩ ይረዳል እንዲሁም የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታይ ልጆች ትምህርት ልጆች መሰረታቸውን ሳይለቁ እንዲያድጉ እና ስለ ሀይማኖታቸው ጥልቅ እውቀት እንዲኖራቸው ያረጋል። ለተለያዩ ተማሪዎች እንደየ እውቀታቸው እና እድሜያቸው የተለያየ ክፍልም ከተለያዩ መማርያ መፃህፍት ጋር ያዘጋጀን ሲሆን ትምህርታቸውንም እንዳጠናቀቁ እንደየ ደረጃቸው የኦንላይን ሰርተፊኬት የምናበረክት ይሆናል። ቀጠሮ ይያዙ ወይም በስልክ እና በ ኢ-ሜይል ያግኙን።

ህዝቅኤል እና ብርሃኑ
መስራች እና ስራ አስኪያጅ

የአጀማመር ሂደት

ተማሪዎች ወይም የተማሪዎች ወላጅ ቀጠሮ የመያዣ ቅጹን በመሙላት ወይም አድራሻ ገጽ ላይ በሚገኙት አድራሻዎቻችን ሁሉ የሚያገኙን ሲሆን ተማሪዎች በመጀመርያ በፈተና ደረጃቸው ( ጀማሪ፣ መካከለኛ፣ ብቁ) ተለይቶ በየ ክፍሉ ይደለደላሉ ። በተለያየ ሰዓት ክፍሎች ስላሉን ስለ ሰዓት አይጨነቁ ።

አሁኑኑ ይጀምሩ

እውቅ አስተማሪዎቻችን

ሀና ሙሉጌታ

አማርኛ አስተማሪ

ጌታሁን ቢረዳ

ሒሳብ አስተማሪ

ዮሃና አብረሀም

ትግርኛ ኣስተማሪ